አምላክ በጥበብና በሞገስ እንዴት ያድጋል?

 


16. የሉቃስ ወንጌል 2፡52 ላይ“ኢየሱስም በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት አደገ፡፡” ይላል፡፡ ኢየሱስ አምላክ ከሆነ እንዴት አምላክ በጥበብ ያድጋል? ከማደጉ በፊትስ? ፍፁም የሆነው አምላክ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡ የቀድሞውንም፤ የአሁኑንም ሆነ የወደፊቱን ያውቃል ፡፡ ኢየሱስ ግን ከዚህ በኋላ ነው በጥበብ ያደገው፡፡ ታድያ እንዴት አምላክ ይሆናል?

በመለኮቱ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ጥበብ ነው፡፡ ስለዚህ በጥበብ ማደግ አያስፈልገውም (1ቆሮንቶስ 1፡24)፡፡ ይህ ጥቅስ ስለ ኢየሱስ ሰብዓዊ ባሕርይ እንጂ ስለ መለኮታዊ ባሕርዩ የሚናገር አይደለም፡፡ ኢየሱስ ፍፁም ሰው ስለነበረ የሰው አካልና የሰው አዕምሮ ነበረው፡፡ ስለዚህ በቁመት ማደግ እንዳስፈለገው ሁሉ በጥበብም ማደግ አስፈልጎታል፡፡

 

 

ለአሕመዲን ጀበል 303 ጥያቄዎች የተሰጠ መልስ ማውጫ