አምላክ “እኔ እግዚአብሔር አልለዋወጥም” ካለ፤ ኢየሱስ አንድ ጊዜ “ፍፁም አምላክ” በሌላ ጊዜ “ፍፁም ሰው” እንዴት ሊሆን ይችላል?

 


25. ኢየሱስ አንድ ጊዜ “ፍፁም አምላክ” በሌላ ጊዜ “ፍፁም ሰው” ይሆናል ካልን በክርስቶስ ማንነት ላይ ብዥታው ይጎላል፡፡ ምክንያቱም አምላክ “እኔ እግዚአብሔር አልለዋወጥም፡፡” ሲል በሚልክያስ 3:6 ላይ ገልጿል፡፡ ታዲያ አምላክ ይህንን ቃሉን አጠፈ ማለት ነውን?

ኢየሱስ አንድ ጊዜ “ፍፁም አምላክ” በሌላ ጊዜ “ፍፁም ሰው” ይሆናል ብሎ የሚያምን ክርስቲያን የለም፡፡ አሕመዲን ይህንን ቅጥፈት ከራሳቸው የተሳሳተ መረዳት ነው ያገኙት፡፡ ይህ ደግሞ ቁጭ ብሎ ያለማንበብና ያለመማር ውጤት ነው፡፡ ኢየሱስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ነው ስንል አንድ ጊዜ ሰው ሌላ ጊዜ ደግሞ አምላክ ይሆናል ማለታችን ሳይሆን ድህረ ትስብዕቱ እነዚህ ሁለቱ ባሕርያት ሳይነጣጠሉና ሳይደባለቁ በአንዱ የኢየሱስ ማንነት ውስጥ በአንድ ጊዜ ይኖራሉ ማለታችን ነው፡፡ ቅድመ ትስብዕቱም ሆነ ድህረ ትስብዕቱ የኢየሱስ መለኮታዊ ባሕርይ ስላልተለወጠ እግዚአብሔር አለመለወጡን ከሚናገሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር የሚጣረስ ምንም ነገር የለም፡፡ ነገር ግን እስላማዊ ትውፊቶች አላህ እንደሚለዋወጥ ስለሚናገሩ ጸሐፊው ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ የሚያመልኩትን አምላክ በተመለከተ እንደ መስፈርት ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸው ያጠራጥራል፡፡ የግርጌ ማስታወሻውን ይመልከቱ፡፡[3]

 

 

ለአሕመዲን ጀበል 303 ጥያቄዎች የተሰጠ መልስ ማውጫ