ኢየሱስ ሰው ከሆነ አምላክ፣ አምላክ ከሆነ ደግሞ ሰው መሆን እንዴት ይችላል?

 


33. እንደ ክርስትና እምነት “ኢየሱስ ሰውም አምላክም ነው”፡፡ ኢየሱስ ፍጡር ነውን? አይደለም” ከሆነ ምላሽዎ ኢየሱስ ሰው አይደለም ማለት ነው፡፡ “አዎን” ካሉ ደግሞ “አምላክ” አይደለም፡፡ ምክንያቱም አምላክ ፍጡር አይደለምና፡፡ ታዲያ ምን ሊሆን ነው?

የኢየሱስ ሰብዓዊ ባሕርይ ከተሠግዎ በኋላ የተገኘ ነው፡፡ መለኮቱ ግን በጊዜ ባልተገደበ ዘለዓለማዊነት ከአብ የተገኘ በመሆኑ ፈጣሪ እንጂ ፍጡር አይደለም፡፡ ኢየሱስ ሰብዓዊና መለኮታዊ ባሕርያት ቢኖሩትም አንድ ማንነት እንጂ ሁለት ማንነቶች የሉትም፡፡ ይህ አንዱ ማንነት ደግሞ መለኮት በመሆኑ ፈጣሪ እንጂ ፍጡር አይደለም፡፡ ሁለቱ የኢየሱስ ባሕርያት ያልተነጣጠሉና ያልተደባለቁ በመሆናቸው “አምላክ ከሆነ ሰው አይደለም፤ ሰው ከሆነ ደግሞ አምላክ አይደለም” የሚል አመክንዮ አይሠራም፡፡ ሁለቱም ባሕሪያት በአንድ ጊዜ አንድ ላይ እንዳይኖሩ የሚከለክል ምንም ምክንያት የለም፡፡ እንዲህ ዓይነት ጥያቄ የክርስትናን አስተምህሮ ከተረዳ ሰው ፈፅሞ አይጠበቅም፡፡

 

 

ለአሕመዲን ጀበል 303 ጥያቄዎች የተሰጠ መልስ ማውጫ