ኢየሱስ ያለ አባት በመወለዱ “አምላክ” ከሆነ አዳም ምን ሊባል ነው?

 


87. ኢየሱስ ያለ አባት በመወለዱ “አምላክ” ከሆነ ያለ አባትና እናት የተፈጠረዉን አዳም ትልቅ “አምላክ” ልንለዉ ለምን አልደፈርንም?

ኢየሱስ አምላክ የሆነው ያለ አባት በመወለዱ ምክንያት እንደሆነ ክርስትና ስለማያስተምር ይህ የአሕመዲን ጥያቄ ዕውቀት ከማጣት የመነጨ ነው፡፡ ኢየሱስ አምላክ በመሆኑ ያለ አባት ተወለደ እንጂ ያለ አባት ስለተወለደ አምላክ አልሆነም፡፡ አዳም የመጀመርያው ሰው በመሆኑ ምክንያት ያለ እናት እና አባት እንደ ተፈጠረ ያስማማናል፡፡ ነገር ግን ዒሳ ያለ አባት ከእናት ብቻ መወለዱ ለምን ይሆን? ሙስሊሞች ምናልባት ለሰው ልጆች ምልክት እንዲሆን ነው የሚል መልስ ይሰጡ ይሆናል፡፡ በእምነት እንጂ በተግባር ሊረጋገጥ የማይችለውን መንገድ መጠቀም ለሰው ልጆች ምልክት ሊሆን የሚችለው እንዴት ሆኖ ነው?