በመጽሐፍ ቅዱስ አምላክ “አንድ” እንጂ “ሦስትም አንድም” አይልም!

 


  1. በመጽሐፍ ቅዱስ አንድም ስፍራ ላይ አምላክ “አንድ” እንጂ “ሦስትም አንድም” ሳይባል መጠቀሱ “አምላክ አንድም ሦስትም” የሚለውን ንግግር መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለ መሆኑን አያሳይምን?

“ተውሂድ” የተሰኘው የአላህ አንድነት አስተምህሮ ሦስት ክፍሎች እንዳሉት በቁርኣን ውስጥ ቃል በቃል አለመጠቀሱ ትምህርቱ ቁርአናዊ አለመሆኑን እንደማያሳይ ሁሉ “እግዚአብሔር ሦስትም አንድም” ተብሎ ቃል በቃል አለመጻፉ አስተምህሮው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አለመሆኑን አያሳይም፡፡ ሥላሴን የሚገልፁ እጅግ በርካታ ጥቅሶች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ (ማቴዎስ 3፡16-17፣ 28፡19፣ ዮሐንስ 14፡18፣ 1ቆሮንቶስ 12፡4-6፣ 2ቆሮንቶስ 13፡14፣ ዘፍጥረት 1፡1-2፣ 1፡26፣ ዘፍጥረት 3፡22፣ 1ጴጥሮስ 1፡1-2፣ ሮሜ 14፡17-18፣ ዮሐንስ 10፡30)፡፡