በመስቀሉ ላይ የተጻፈው ጽሕፈት በአራቱ ወንጌላት ለምን ተለያየ?
አራቱም ወንጌላት በመስቀሉ ላይ ስለነበረው ጽሕፈት የተለያየ ዘገባ ማቅረባቸው ስህተት መኖሩን ያመለክታልን? በፍጹም! ሉቃስም ሆነ ዮሐንስ በኢየሱስ መስቀል ላይ የነበረው ጽሕፈት በሦስት ቋንቋዎች ማለትም በግሪክ፣ በላቲን እና በዕብራይስጥ ተጽፎ እንደነበር ይነግሩናል። ስለዚህ ሦስቱ የወንጌል ጸሐፊያን እያንዳንዳቸው ከተጻፉት ሦስት ቋንቋዎች አንዱን መርጠው ጠቅሰዋል፣ አራተኛው ደግሞ በሦስቱም ቋንቋዎች ውስጥ የነበሩትን የጋራ ቃላት መርጧል ብሎ ማሰብ ምክንያታዊ ነው።
ይህ መላ ምት ሊረጋገጥ ይችላልን? ከሆነስ፣ ማን የትኛውን ቋንቋ እንደጠቀሰ በእርግጠኝነት መናገር ይቻል ይሆን?
ጽሕፈቶቹ
እያንዳንዱ ጸሐፊ ስለ ጽሕፈቱ አጀማመር እንዴት እንደገለጸ እንመልከት፦
-
ማቴዎስ 27:37፦ “…የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።”
-
ማርቆስ 15:26፦ “የክሱ ጽሕፈትም … የሚል ተጽፎ ነበር።”
-
ሉቃስ 23:38፦ “…በግሪክና በሮማይስጥ በዕብራይስጥም ፊደል የተጻፈ ጽሕፈት ደግሞ በእርሱ ላይ ነበረ።”
-
ዮሐንስ 19:19፦ “ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው”
እነዚህ ሁሉ መግቢያዎች እንደሚለያዩ ልብ በሉ። ማርቆስ ጽሕፈት መኖሩን ይነግረናል፤ ማቴዎስ ከራሱ በላይ እንደተሰቀለ ይገልጻል፤ ሉቃስ በሦስት ቋንቋዎች መጻፉን ሲገልጽ፣ ዮሐንስ ደግሞ ጲላጦስ እንዳስጻፈው ይነግረናል። እያንዳንዱ ጸሐፊ የተለያየ ነገር ቢናገርም ሁሉም መረጃዎች ትክክል ናቸው።
አራቱ የወንጌል ዘገባዎች ልዩነታቸውንና አንድነታቸውን በቀላሉ ለማየት በሚያስችል መልኩ ከዚህ በታች ቀርበዋል፦
| ማቴዎስ 27:37 | ይህ | ኢየሱስ | የአይሁድ ንጉሥ ነው | |
| ማርቆስ 15:26 | የአይሁድ ንጉሥ | |||
| ሉቃስ 23:38 | ይህ | የአይሁድ ንጉሥ ነው | ||
| ዮሐንስ 19:19 | የአይሁድ ንጉሥ | የናዝሬቱ ኢየሱስ |
ሦስቱ ቋንቋዎች የነበራቸው ፋይዳ ምን ነበር?
ሮማውያን አንድ ሰው ለምን እንደተገደለ ለማሳወቅ በኖራ በተቀባ ሰሌዳ ላይ ጽፈው በመስቀል ላይ የመለጠፍ ልማድ ነበራቸው። ሁልጊዜ ባይሆንም አንዳንድ ጊዜ ሦስት ቋንቋዎችን ይጠቀሙ ነበር።
-
ላቲን፦ የሮም መንግሥት ይፋዊ ቋንቋ ሲሆን፣ የሰውን አስተዳደር፣ ሥልጣንና ድል አድራጊነትን ይወክላል።
-
ግሪክ፦ የባሕልና የጥበብ ዓለም አቀፍ ቋንቋ ሲሆን፣ የሰውን ጥበብ፣ ሥነ-ጥበብና ንግድን ይወክላል።
-
ዕብራይስጥ፦ የአይሁድ የሃይማኖት ቋንቋ ሲሆን፣ የእግዚአብሔርን ሕግና እግዚአብሔር ራሱን ለሰው የገለጠበትን መንገድ ይወክላል።
በእግዚአብሔር አሠራር ኢየሱስ ሲሰቀል እነዚህ ሁሉ ሰብአዊና መለኮታዊ ተቋማት መልእክት ደርሷቸዋል። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?
የሮማው ገዥ ጲላጦስ ጽሕፈቱን በላቲን ቋንቋ አዝዞ፣ ግድያውን የሚመራው የመቶ አለቃ ደግሞ ትእዛዙን ወደ ሌሎቹ ቋንቋዎች አስተርጉሞ እንዲጻፍ አድርጓል ቢባል ያስኬዳል። “የአይሁድ ንጉሥ” የሚሉት ቃላት ጲላጦስ በአይሁድ ላይ የሰነዘረው ስላቅ ሲሆን፣ “የናዝሬቱ” የሚለውን በመጨመር ደግሞ ንጉሣቸው የተናቀ የገሊላ ሰው መሆኑን በመግለጽ ይበልጥ ሊያበሳጫቸው ፈልጓል።
ዮሐንስ
ገዢው ጲላጦስን፣ ናዝሬትን እንዲሁም ጽሕፈቱን “ታይትል” (Titulus በላቲን) ብሎ የጠቀሰው ዮሐንስ ብቻ በመሆኑ እርሱ የጠቀሰው የላቲኑን ትርጉም እንደሆነ ግልጽ ነው። የላቲኑ ጽሕፈት እንዲህ ይላል፦
IESUS NAZARENVS REX IVDAEORVM
ይህ የላቲን ጽሕፈት መሆኑን የሚያረጋግጠው ሌላው ማስረጃ ጥንታዊት ቤተክርስቲያን የዚህን ጽሕፈት የመጀመሪያ ፊደላት በመውሰድ “INRI” የሚለውን ምልክት መጠቀሟና ይህም በብዙ ጥንታዊ ስዕሎች ላይ መታየቱ ነው።
ሉቃስ
ሉቃስ ከፍተኛ ትምህርት የቀሰመ (ሐኪም) የነበረ ሲሆን (ቆላስይስ 4:14)፣ ወንጌሉን የጻፈውም ለተከበረው ግሪካዊው “ቴዎፍሎስ” ነው። ስለዚህ ሉቃስ የጠቀሰው የግሪኩን ጽሕፈት ነው ብሎ ማሰብ ምክንያታዊ ነው፦
ΟΥΤΟΣ ΕΣΤΙΝ Ο ΒΑΣΙΛΕΥΣ ΤΩΝ ΙΟΥΔΑΙΩΝ
ማቴዎስ
ማቴዎስ የጻፈው ለአይሁድ ሲሆን፣ ኢየሱስ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶች ፍጻሜ መሆኑን ለማሳየት ብዙ ጥቅሶችን ተጠቅሟል። ስለዚህ ማቴዎስ የጠቀሰው የዕብራይስጡን ጽሕፈት ነው ማለት ይቻላል።
זה ישוע מלך היהודים
ማርቆስ
የማርቆስ ወንጌል ከአራቱም አጭር ሲሆን፣ ትኩረቱም ኢየሱስ ከተናገረው ይልቅ ባደረገው ላይ ነው። ለምሳሌ የኢየሱስን ልደትና የተራራውን ስብከት አልጠቀሰም። ማርቆስ እንደ ልማዱ ጽሕፈቱን አሳጥሮ በሦስቱም ቋንቋዎች ውስጥ የነበሩትን የጋራ ቃላት ማለትም “የአይሁድ ንጉሥ” የሚለውን ብቻ ጠቅሷል።
ሰሌዳው
አስገራሚው ጉዳይ ይህ ነው! የላቲኑ ጽሕፈት ኦፊሴላዊ የክስ መግለጫ በመሆኑ በመጀመሪያው የሰሌዳው መስመር ላይ የሰፈረው እርሱ እንደነበረ ምንም ጥርጥር የለውም። ይህም የሰሌዳው ርዝመት ምን ያህል መሆን እንዳለበት፣ እንዲሁም ጽሕፈቱ በአንድ መስመር እንዲያልቅና ከሩቅ ለሚመለከተው ሕዝብ (ዮሐንስ 19:20) በግልጽ እንዲታይ የሚያስፈልገውን የፊደላት መጠን ይወስናል።
በዚያ ዘመን እንደ ዛሬው በቃላት መካከል ክፍተት አይጠቀሙም ነበር። የዮሐንስ የላቲን ጽሕፈት ያለ ምንም ክፍተት 26 ፊደላትን ይይዛል። የሉቃስ የግሪክ ጽሕፈት ደግሞ 30 ፊደላት ስላሉት ከላቲኑ ትንሽ አነስ ባሉ ፊደላት መጻፍ ይኖርበታል። በግሪኩ ቋንቋ “የናዝሬቱ ኢየሱስ” የሚሉትን ተጨማሪ 16 ፊደላት ለማስገባት ሰሌዳው በቂ ቦታ አይኖረውም።
የማቴዎስ የዕብራይስጥ ጽሕፈት ደግሞ 19 ፊደላት ብቻ ነበሩት (ምክንያቱም ዕብራይስጥ አናባቢዎችን ስለማይጽፍ)። ወደ ዕብራይስጥ የተረጎመው ሰው አይሁዳዊ ሊሆን ስለሚችል “የናዝሬቱ” የሚለውን መጨመር አስፈላጊ ሆኖ አልታየው ይሆናል።
ይህንን ሁሉ ስናጠቃልል፣ በመስቀሉ ላይ የነበረው ሰሌዳ ላቲኑ ከላይ፣ ከዚያም ግሪኩና ዕብራይስጡ ተከታትለው የሰፈሩበት የመሆን ዕድሉ ሰፊ ነው። በምስል ብናስቀምጠው ይህንን ይመስላል፦

ደራሲ፦ Russell M. Grigg. First published in Apologia 3(2):17-18, 1994
