ኢየሱስ የእግዚአብሔር ከሆነ እንዴት አምላክ ይሆናል?

 


13. 1ኛ ቆሮንቶስ 3፡23 “እናንተም የክርስቶስ ናችሁ፤ ክርስቶስም የእግዚእልብሔር ነው” ይላል፡፡ ክርስቶስ የእግዚያብሔር መሆኑ በዚህ ጥቅስ ተገልጿል፡፡ ታዲያ “የእግዚአብሔር” እና “እግዚአብሔር” አንድ ናቸውን? እንዲያማ ከሆነ በጥቅሱ መሠረት “እናንተ የክርስቶስ ናችሁ፡፡” ስለተባለ ክርስቲያኖችና ክርስቶስ አንድ ናቸው ማለት ነዋ?

አዲስ ኪዳን አውዱ ግልፅ ካላደረገ በስተቀር “እግዚአብሔር” ሲል አብን ማለቱ መሆኑን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ገልፀናል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ የእግዚአብሔር መሆኑ መገለፁ እርሱና አብ በአካል ልዩ መሆናቸውን ያመለክታል፡፡ ኢየሱስ ከአብ ጋር በመለኮት አንድ መሆኑንና ወልድ መሆኑን የሚያሳዩ ብዙ ጥቅሶች ስላሉ ይህንን ጥቅስ ኢየሱስ በአካል ከአብ ልዩ መሆኑን ከማመልከት ባለፈ አምላክ መሆኑን ወይም ከአብ ጋር አንድ መሆኑን ለማመልከት አንጠቀምም፡፡