ሥላሴ የኢየሱስ እውነተኛ አስተምህሮት ከነበረ ለምንድን ነው ኢየሱስ ያላብራራው?

 


15. ሥላሴ የኢየሱስ እውነተኛ አስተምህሮት ከነበረ ለምንድን ነው አንድም ክርስቲያን ሊፈታው ያልቻለውን ምስጢር ያን ታላቅ የማስተማር ችሎታውን ተጠቅሞ ኢየሱስ ያላብራራው? ሰውንም ግራ ከማጋባት “ሁከት” ያልገላገለው?

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ እንዲህ ብሎ ነበር፡- “የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም፡፡ ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል” (ዮሐንስ 16፡12-15)፡፡ ጌታችን ስለ አብ፣ ስለ ራሱና ስለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ነገሮችን ያስተማረ ቢሆንም ነገር ግን በወቅቱ ሐዋርያቱ ሊገነዘቡት በሚችሉት መጠን ነበር፡፡ ሐዋርያቱ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ አይሁድ ከዚያ ቀደም ያልተረዱትን የእግዚአብሔርን ሥላሴያዊነት እና የኢየሱስ ክርስቶስን ተልዕኮ ዓላማ በሙላት ተረድተዋል፡፡ በስፋትና በጥልቀትም አስተምረዋል፡፡