አምላክ “አንድም ሦስትም ነው” የሚል አንድ ጥቅስ እንኳ አለ?

 


21. አምላክ “አንድም ሦስትም ነው” የሚል አንድ ጥቅስ እንኳ ማቅረብ ሳንችል እንዴት በሰው አመለካከት ላይ ተንተርሰን አምላክን “ሦስትም አንድም” ልንል ይቻለናል?

የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት ከአንድ ጥቅስ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሰፈረው አጠቃላይ መረጃ የተገኘ ነው፡፡ እውነትን የሚፈልግ አስተዋይ ሰው አጠቃላይ መረጃዎችን በማገናዘብ እንጂ በአንድ ጥቅስ ላይ በመንጠልጠል እምነቱን አይመሰርትም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ አብ አምላክ መሆኑን (ዮሐንስ 17፡3፣ 1ቆሮንቶስ 8፡8)፣ ወልድ አምላክ መሆኑን (ኢሳይያስ 6፡9፣ ዮሐንስ 1፡1፣ 20፡28፣ ሮሜ 9፡5፣ ቲቶ 2፡13፣ ዕብራውያን 1፡8፣ 2ጴጥሮስ 1፡1)፣ መንፈስ ቅዱስም አምላክ መሆኑን ይናገራል (የሐዋርያት ሥራ 5፡3-4፣ ዮሐንስ 5፡3-4፣ 2ቆሮንቶስ 3፡17)፡፡ ነገር ግን አንድ አምላክ ብቻ እንዳለ ያስተምራል (ዘዳግም 6፡4፣ ኢሳይያስ 43፡10፣ 44፡8፣ ኤርምያስ 10፡10፣ ያዕቆብ 2፡19)፡፡ ሥላሴ የሚለው ቃል ይህንን መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የሚገልፅ የሥነ መለኮት ቃል ነው፡፡