የሃጢአት ስርየትስ ለማን ነው ይሰጥ ዘንድ የተላከው? ለእስራኤል!

 


60. የሐዋርያት ስራ 5፡31 ላይ “እርሱም ለእስራኤል ንስሀንና የኃጢአትን ሰርየት ይሰጥ ዘንድ፣ እግዚአብሔር የሁሉ ራስና አዳኘ አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው፡፡” ይላል፡፡ እግዚአብሔር በቀኙ ከፍ ሳያደርገውስ በፊት ኢየሱስ ምን ነበር? የሃጢአት ስርየትስ ለማን ነው ይሰጥ ዘንድ የተላከው? ለእስራኤል! ታዲያ ምን ነካቸው?

ለጥያቄው የመጀመርያ ክፍል መልስ ቁጥር 58ን ይመልከቱ፡፡ አሕመዲን በቃለ አጋኖ በመጮኽ ኢየሱስ ለእስራኤል ብቻ ንስሐና የኃጢአትን ስርየት የሚያመጣ እንደሆነ ለማስመሰል ቢሞክሩም ጥቅሱ ግን ለእስራኤል ብቻ እንደማይል ልብ ይሏል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም አዳኝ መሆኑና የወንጌሉ መልዕክት ለዓለም ሁሉ የተሰጠ መሆኑ በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ተጠቅሷል (ማቴዎስ 24፡14፣ 28፡19-20፣ ማርቆስ 16፡15፣ ዮሐንስ 1፡29፣ 3፡17፣ 4፡42፣ 6፡51፣ 8፡12፣ 11፡27፣ 17፡18፣ 1ጢሞቴዎስ 1፡15፣ 1ዮሐንስ 4፡14፣)፡፡